ኢ/ር ታከለ ኡማ እና ሌሎች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ጊቤ ይባሬ ቀበሌ የመሰረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል። SUN Mining and Trading Plc የተባለ ሃገር በቀል ኩባንያ በ800 ሚሊዮን ብር የስራ ካፒታል የመደበ ሲሆን ለ1500 ዜጎች በቀጥታና በተዘዋዋሪ የስራ እድል ይፈጥራል።በ10 ወራት ውስጥ የፋብሪካ ተከላው የሚያጠናቅቅ ሲሆን በሰአት 150 ቶን የድንጋይ ከሰል ያጥባል።ኩባንያው […]
ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሃብት ውሃ መስኖና ኢነርጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር የ10 ወራትን አፈጻጸሙን ገምግሟል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ ኩባንያዎች ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ በገቡት የስራ ውል መሰረት ወደ ስራ ያልገቡ የምርትና የምርመራ ፈቃዶችን ውላቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡ የማዕድን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ እንደተናገሩት አላቂ የሆነው የማዕድን […]
የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ለክልል የማዕድን ፈቃድ ባለሙያዎች የካዳስተር አጠቃቀም ስልጠና ሰጠ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማዕድን ፈቃድን ለማስተዳደር ካዳስተር በመጠቀም ለባለፈቃዶች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ አገልግሎቱ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተጨማሪ በሁሉም ክልሎች ወጥ የሆነ የፈቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር እንዲኖር ለማስቻል ከክልል ለተውጣጡ የዘርፉ ባሙያዎች ለአንድ ሳምንት ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ካዳስተር ፈቃድ የተሰጠባቸው እና ያልተሠጠባቸውን ቦታዎች በቀላሉ መለየት ያስችላል፡፡ […]
የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት ለማካሄድ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ። ስምምነቱን የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና አቶ ወንድማገኘሁ ነገራ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሚያዚያ 29 ቀን 2013 ዓ.ም በሀያት ሬጀንሲ ሆቴል በተካሄደው መርሃግብር ላይ ተፈራርመዋል። የመግባቢያ ሰነዱ ዋና ዓላማ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ […]
በማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ካሉት 97 የምርመራ ፈቃዶች ለ27 በእቅዳቸው መሰረት መስራት ባለመቻላቸው ውላቸው ሲቋረጥ ለ3 ፈቃዶች ደግሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል። ለቀንጢቻ ታንታለም እና ለቱሊካፒ የወርቅ ኩባንያዎች በውላቸው መሠረት እንዲሠሩ በልዩ ሁኔታ የጊዜ ገደብ የተሠጣቸው ሲሆን በአግባቡ ካልሠሩ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚወሠድ ይሆናል ተብሏል።ባለፉት 10 ወራትም ከዘርፉ 513.92 ሚሊዮን ዶላር ከውጭ ንግድ ገቢ ማግኘት ተችሏል።
የፌዴራል የስነምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን በማዕድን ዘርፍ የሚስተዋለውን ተግዳሮቶችን “national study on the prevention of corrupt practices in the mining sector” በሚል ባስጠናው ጥናት ላይ የሚንስቴር መስሪያ ቤቱ እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡ በጥናቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ማዕድን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ ‹‹ማዕድን የማይተካ የተፈጥሮ ሃብት በመሆኑ ዘርፉ […]
የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በሚኔራል፣ በፔትሮሊየምና ፔትሮኬሚካል ኢንጂነሪግ የሁለተኛ ዲግሪ የስረዓተ ትምህርት ቀረጻ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው፡፡ የትምህርት ዘርፎቹ በዘርፍ ያለውን የባለሙያ እጥረት የሚፈታ ነው፡፡ የትምህርት አሰጣጡ ከንድፈ-ሃሳብ በዘለለ በተግባር የሚሰጥ ነው፡፡ በቀጣዮቹ 10 አመታት ከመላው ሀገሪቱ የተውጣጡ 675 ተማሪዎችን ለማስተማር እቅድ ተይዟል፡፡ በዘንድሮው አመትም 50 ተማሪዎችን ለመቀበል የቅድመ […]
ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ለመጠቀም የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡ በወረቀት የሚያዙ መረጃዎች የመበላሸት፣ የመቀደድ፣ የመጥፋት እድላቸው ሰፊ ነው፡፡ ፈልጎ ለማግኘት አዳጋች ናቸው፡፡ ስልጠና የወረቀት ፋይል የመረጃ አያያዝ ስርዓት የሚቀይር ነው፡፡ በሶፍትም ሆነ በሃርድ ኮፒ የሚመጡ መረጃዎችን ማስገባት የሚያስችል አቅም የሚፈጥር ነው፡፡ ስልጠናው ሲጠናቀቅ ሙሉ በሙሉ ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓቱ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የመዝገብ […]
በሐገራችን ለ45ኛ በዓለም ደግሞ ለ110ኛ ጊዜ የተከበረውን የሴቶች ቀን ማርች 8 አከበረ፡፡ የዘንድሮው የዓለም የሴቶች ቀን እየተከበረ ያለው ‹‹የሴቶችን መብት የሚያስከብር ማህበረሰብ እንገንባ›› የሚል መሪ ነው፡፡ የማዕድን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ በመክፈቻ ንግግራቸው በሴቶች ላይ የሚደርሱ ዘርፈ ብዙ ጥቃቶችን ለማስቆም በተለይም ለእኩል ስራ እኩል ክፍያ በማለት በ19ኛው ክፍለ ዘመን ትግላቸውን በመጀመር ዛሬ ለደረስንበት […]