የማዕድን ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሐገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል፡፡ ለውይይቱ “የድህረ ጦርነት መዛነፎችና እርምቶች” በሚል ርዕስ በድህረ ጦርነት ያሉ ተስፋዎችና ስጋቶች ከክልሎች ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም ከብሔራዊ መግባባትና ከሀገር ግንባታ አንጻር የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሄዶበታል፡፡ ሰራተኞቻች ገንቢ የሆነ፣ ለሀገር ግንባታ ፋይዳው የጎላ ሀሳቦችን አንስተዋል፡፡ የማዕድን ሚኒስቴር ሚንስትር ኢንጅነር ታከለ ኡማ […]
ባለፉት አምስት ወራት ከማዕድን የወጪ ንግድ በተለይም ከወርቅ 241 ሚሊየን ዶላር ገቢ ማግኘት ተችሏል። አሁን ካለንበት ሀገራዊ ሁኔታ በተለይም በማዕድን አካባቢዎች የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮችን ተቋቁመን የተመዘገው ውጤት አበረታች ነው። ያሉ ችግሮችን እየፈታንና እየሄድንበት ያለውን መንገድ አጠንክረን ከቀጠልን የማእድን ምርታችን የኢኮኖሚያችን ማገር መሆን እንደሚችል እየታየ ያለው ውጤት ማሳያ ነው ሲሉ የማዕድን ሚኒስቴር ሚንስትር ኢ/ር ታከለ ዑማ […]
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው እለት ባኪያሄደው ስብሰባ በሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የቀረቡለትን ሰባት የማአድን ምርት ፈቃዶች አጽድቋል፡፡ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ስምምነቶቹ የሚኖራቸውን የአዋጭነት፣ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እንዲሁም የኩባንያዎቹን ካፒታል በዝርዝር ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ያቀረበ ሲሆን ምክርቤቱም ይህን በመገንዘብ ስምምነቶቹን አጽድቆልናል፡፡ የሚፈረሙት ስምምነቶች ለሀገራችን ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ በማስገኘት በኩልም ይሁን ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር በኩል ትልቅ ድርሻ የሚኖራቸው ይሆናል፡፡ከምንሰጣቸው ሰባት […]
የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ለክልል የማዕድን ፈቃድ ባለሙያዎች የካዳስተር አጠቃቀም ስልጠና ሰጠ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማዕድን ፈቃድን ለማስተዳደር ካዳስተር በመጠቀም ለባለፈቃዶች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ አገልግሎቱ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተጨማሪ በሁሉም ክልሎች ወጥ የሆነ የፈቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር እንዲኖር ለማስቻል ከክልል ለተውጣጡ የዘርፉ ባሙያዎች ለአንድ ሳምንት ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ካዳስተር ፈቃድ የተሰጠባቸው እና ያልተሠጠባቸውን ቦታዎች በቀላሉ መለየት ያስችላል፡፡ […]