Category: News

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዘርፉን የሰባት ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ከተቋሙና ከተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ጋር የዘርፉን የሰባት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ቀርቧል። ከባለፈው በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ከዘርፉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል። በተደረገው ተቋማዊ ሪፎርም ተግባራት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የማዕድን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ስመኝ ገልጸዋል። መንግስት ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት የሠጠው በመሆኑ አመራሩና ሠራተኛው በጋራ ተናቦ […]
Read More

የድንጋይ ከሰልን ለማቅረብ በቅንጅት መስራት ይገባል ተባለ

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር እና የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከሲሚንቶ ፋብሪካ ሃላፊዎችና ከድንጋይ ከሰል አምራቾች ጋር ውይይት አካሄዱ፡፡ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች የድንጋይ ከሰልን በሃይል ምንጭንት ይጠቀማሉ፡፡ የድንጋይ ከሰልን ከውጭ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማስገባት የሚጠቀሙት ፋብሪካዎች በአሁኑ ጊዜ በሐገር ውስጥ የሚመረተውን የድንጋይ ከሰል ከ40 እስከ 60 ፐርሰንት መጠቀም የጀመሩ ሲሆን በሂደት ሙሉ በሙሉ የአገር ውስጥ የድንጋይ ከሰል ለመጠቀም የሚያስችል […]
Read More

በማዕድንና ነዳጅ ሚ/ር የማዕድን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በክብርት ወ/ሮ ስመኝ ውቤ የተመራ የልዑካን ቡድን በምዕራብ አፍሪካዊት ሀገር ማሊ የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት አደረገ

ጉብኝት ያዘጋጀው ‘Allied Gold Cop’ የተባለ የማዕድን ልማት ኩባንያ ሲሆን ኩባንያው በቤንሻንጉል-ጉምዝ፣ አሶሳ ዞን፣ ኩርሙክ ወረዳ ዲሽ እና አሻሽሬ በተባሉ ቦታዎች ላይ በከፍተኛ ደረጃ ሊለሙ የሚችሉ ሁለት (2) የወርቅ ክምችት ምርመራ በማድረግ በቅርቡ ወደ ልማት ለመሸጋገር የምርት ፈቃድ ለመውሰድ የተዘጋጀ ኩባንያ ነው፡፡ ሰባት አባላትን የያዘው የልዑካን ቡድኑ የተውጣጣው ከማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር፣ ከክልሉ ማዕድን ልማት ኤጀንሲ፣ […]
Read More

በማህበረሰብ ልማት ፈንድ የተሰራ ፕሮጀክት ተመረቀ::

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ከድሬዳዋ ከተማ ጋር በመተባበር የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክት አስመረቀ።የማዕድን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ እና የድሬዳዋ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ፕሮጀክቱን መርቀው ከፍተውታል። የተመረቀው ፕሮጀክት በድሬዳዋ ከተማ ለ700 የገንደ ሪጌ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ 1.8 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ሲሆን ገንዘቡ የተገኘው ፓዮኔር ከተባለ የሲሚንቶ ኩባንያ ነው።የማዕድን ኩባንያዎች ማዕድንን […]
Read More

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር የዘርፍ የ10 ዓመት የልማት ዕቅድና የ6ወር ዕቅድ አፈጻጸም ውይይት እየተካሄደ ነው

በማዕድንና ነዳጅ ዘርፎች የማዕድን የምርት አቅርቦት በማሳደግ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እና የ2013 ዓ.ም የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት የተደረገው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሃብት ውሃ መስኖና ኢነርጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ነው ፡፡ የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ሚንስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ ሚኒስቴር መስሪያ […]
Read More

ባለፉት ሶስት ወራት ከማዕድን ዘርፍ ከ178 ሚሊዮን ዶለር በላይ የውጭ ምንዛሬ ተገኘ

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የሶስት ወራት አፈፃፀም በተመለከተ የማአድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኢ/ር ታከለ ኡማ ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል። ወደ ውጭ ተልከው የውጭ ምንዘሬ ካስገኙት ማዕድናት መካከል ፤ ወርቅ፣ታንታለም፣ ኳርትዝ፣ ኢመራልድ፣ ሳፓየር እና እምነበረድ ተጠቃሾች ናቸው ፡፡ ወርቅን በተመለከተ በባህላዊ መንገድ ከሚያቀርቡ አቅራቢዎች 2ሺህ 241 ኪ.ግ ወርቅ ለውጭ ገበያ ቀርቧል፡፡ በእቅድነት ተይዞ የነበረው 251 ኪ.ግ ወርቅ ለውጭ […]
Read More

ኢ/ር ታከለ ኡማ በሲዳማ ክልል በሎጌታ ወንዝ ዳር ወርቅ ለማውጣት በሂደት ላይ የሚገኘውን የሲዳማ ጎልድ ማይኒንግ ተመልክተዋል

ኢ/ር ታከለ ኡማ በሲዳማ ክልል የገናሌ ወንዝ ገባር በሆነው በሎጌታ ወንዝ ዳር ወርቅ ለማውጣት በሂደት ላይ የሚገኘውን የሲዳማ ጎልድ ማይኒንግ ተመልክተዋል። የሲዳማ ጎልድ ማይኒንግ ካምፓኒ ከሁለት ወር በኋሏ ምርቱን ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅት እያደረገ ነው። ካምፓኒው በአካባቢው ተወላጆች እና ነዋሪዎች ባለቤትነት የሚመራ እና የሚበረታታ መሆኑንም ኢ/ር ታከለ ተናግረዋል። አካባቢው ከፍተኛ የመንገድና የመሰረተ ልማት ችግር ያለበት በመሆኑ […]
Read More

ኢ/ር ታከለ ኡማ በአፋር ክልል የሚገኙ የማአድን ልማት ስራዎችን እየተመለከቱ ነው

ኢ/ር ታከለ ከአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ጋር በመሆን የፖታሽ፣ ጨውና ብሮሚን ምርቶች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የማአድን ልማቶችን ተመልክተዋል። ኢ/ር ታከለ አፍዴራ አካባቢ “ታናራሙ ኬሚካልስ” በተባለ የቻይና ኩባንያ እየተገባ የሚገኘው የብሮሚን ፋብሪካ የጎበኙ ሲሆን ፋብሪካው በ57 ሚሊየን ዶላር ወጪ እየተገነባ የሚገኝ ነው። ፋብሪካው “ሀይድሮጅን ብሮማይድ አሲድ” አዘጋጅቶ ለውጪ ገበያ የሚያቀርብ ይሆናል። ፋብሪካው በቅርብ […]
Read More
MoM