Author: momp

ባለፉት ሶስት ወራት ከማዕድን ዘርፍ ከ178 ሚሊዮን ዶለር በላይ የውጭ ምንዛሬ ተገኘ

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የሶስት ወራት አፈፃፀም በተመለከተ የማአድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኢ/ር ታከለ ኡማ ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥተዋል። ወደ ውጭ ተልከው የውጭ ምንዘሬ ካስገኙት ማዕድናት መካከል ፤ ወርቅ፣ታንታለም፣ ኳርትዝ፣ ኢመራልድ፣ ሳፓየር እና እምነበረድ ተጠቃሾች ናቸው ፡፡ ወርቅን በተመለከተ በባህላዊ መንገድ ከሚያቀርቡ አቅራቢዎች 2ሺህ 241 ኪ.ግ ወርቅ ለውጭ ገበያ ቀርቧል፡፡ በእቅድነት ተይዞ የነበረው 251 ኪ.ግ ወርቅ ለውጭ […]
Read More

ኢ/ር ታከለ ኡማ በሲዳማ ክልል በሎጌታ ወንዝ ዳር ወርቅ ለማውጣት በሂደት ላይ የሚገኘውን የሲዳማ ጎልድ ማይኒንግ ተመልክተዋል

ኢ/ር ታከለ ኡማ በሲዳማ ክልል የገናሌ ወንዝ ገባር በሆነው በሎጌታ ወንዝ ዳር ወርቅ ለማውጣት በሂደት ላይ የሚገኘውን የሲዳማ ጎልድ ማይኒንግ ተመልክተዋል። የሲዳማ ጎልድ ማይኒንግ ካምፓኒ ከሁለት ወር በኋሏ ምርቱን ለገበያ ለማቅረብ ዝግጅት እያደረገ ነው። ካምፓኒው በአካባቢው ተወላጆች እና ነዋሪዎች ባለቤትነት የሚመራ እና የሚበረታታ መሆኑንም ኢ/ር ታከለ ተናግረዋል። አካባቢው ከፍተኛ የመንገድና የመሰረተ ልማት ችግር ያለበት በመሆኑ […]
Read More

ኢ/ር ታከለ ኡማ በቤኔሻንጉል ጉምዝ ክልል የሚገኙ የማዕድን ማውጫ ቦታዎችን ተመልክተዋል

ኢ/ር ታከለ ኡማ በቤኔሻንጉል ጉምዝ ክልል የሚገኙ የማዕድን ማውጫ ቦታዎችን ከክልሉ ርዕሰመስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ጋር በመሆን ተመልክተዋል። አሻሽሬ አካባቢ ወርቅ በማውጣት ሂደት ላይ የሚገኘውን “አስኮም ማይኒንግ” ከተመለከቷቸው ቦታዎች አንዱ ነው። ካምፓኒው በአካባቢው ወርቅ እና የከበሩ ማዕድናትን በማፈላለግ ሂደት ላይ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ወደ ምርት ለመግባት የሚያስችለውን ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል። ሚንስትሩ ኢ/ር ታከለ ኡማ […]
Read More

ኢ/ር ታከለ ኡማ በአፋር ክልል የሚገኙ የማአድን ልማት ስራዎችን እየተመለከቱ ነው

ኢ/ር ታከለ ከአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ጋር በመሆን የፖታሽ፣ ጨውና ብሮሚን ምርቶች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የማአድን ልማቶችን ተመልክተዋል። ኢ/ር ታከለ አፍዴራ አካባቢ “ታናራሙ ኬሚካልስ” በተባለ የቻይና ኩባንያ እየተገባ የሚገኘው የብሮሚን ፋብሪካ የጎበኙ ሲሆን ፋብሪካው በ57 ሚሊየን ዶላር ወጪ እየተገነባ የሚገኝ ነው። ፋብሪካው “ሀይድሮጅን ብሮማይድ አሲድ” አዘጋጅቶ ለውጪ ገበያ የሚያቀርብ ይሆናል። ፋብሪካው በቅርብ […]
Read More

የማድንና ነዳጅ ፖሊሲ ላይ ውይይት

አዲስ እየተዘጋጀ ባለው የማአድንና ነዳጅ ፖሊሲ ላይ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። በውይይቱ ላይ ሚኒስትሩ ኢ/ር ታከለ ኡማ ተገኝተዋል። በማአድንና ነዳጅ ዘርፍ እስካሁን ፖሊሲ ያልነበረ ሲሆን ዘረፉ በአዋጅና መመሪያዎች የሚመራ ነበር። በፖሊሲ ውይይቱ ላይ የማይክሮ ኢኮኖሚ አማካሪ ቡድን አባላትና በዘርፉ ረጅም አመት ልምድ ያላቸው ሀላፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ። ከዚህ ውይይት በኋላ ፖሊሲው ላይ ከውይይቱ የተገኙ ግብአቶች ተጨምረውበት […]
Read More

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር በነዳጅ ጥራትና ደህንነት ላይ ለክልል ማዕድን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጠ

የስልጠናውን አላማ አስመልከተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ዶ/ር ኳንግ ቱትላም እንደገለጹት የነዳጅና የነዳጅ ውጤቶች አቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከክልል ማዕድን ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለክልሎችና ለከተማ አስተዳደሮች በነዳጅ ማደያዎች ላይ ክትትልና ቁጥጥር እንዲያደርጉ ውክልና የሰጣቸው ሲሆን የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት በዘረፉ ያሉ ችግሮችን ለመቅርፍ ስልጠናው […]
Read More

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ደም ለገሱ

የኢፌዴሪ ማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች “ደማችን ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን” በሚል መሪ ቃል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ለሀገር መከላከያ ሠራዊትም ደም ለግሰዋል፡፡ የህወኃት ጁንታ ቡድን በሰሜን ዕዝ ላይ ያደረሰውን ጥቃት አውግዘዋል፡፡ ህግ ለማስከበር ለተሰማራው ሃይል ደም በመለገስ የአጋርነት ድጋፋቸውን አረጋግጠዋል፡፡ በቀጣይም ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ […]
Read More

ኢ/ ታከለ ኡማ በምዕራብ ወለጋ የሚገኘውን የባህላዊ ወርቅ አምራቾችን ጎበኙ

Biyya Warqee fi Bunaa, Biyya dhadhaa fi dammaa wallagga oolle har’a. Dargaggoon baayy’een oomisha warqee aadaadhaan oomishan dinagdeen of danda’uuf xaaraa jiran jajjaabeessuuf. Dargaggoo baayy’eetu hojii jalqabaniii bu’aa argachuu ifaajaa jiru. Nutis meeshaa oomisha warqee adaaf ta’u deegaruuf ni hojjenna. Rakkoo idoo gurgurtaa warqee kan tures baankiiin daldalaa Itoophiyaa wiirtuu Gimbitti akka irraa bituuf damee […]
Read More

ከማዕድን ዘርፍ ባለፉት አራት ወራት 269.1 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኘ

በአራት ወር ውስጥ ከ3600 ኪ.ግ በላይ ወርቅ ለውጪ ገበያ ቀርቧል። ኢ/ር ታከለ ኡማ በማዕድን ዘርፍ አፈፃፀምና ቀጣይ እቅዶች ዙሪያ ከክልል የማዕድን ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። ኢንጂነር ታከለ ኡማ እንደተናገሩት መንግስት ለዘርፉ ትኩረት ሠጥቶ እየሰራ ሲሆን ባለፉት አራት ወራት 3602.8 ኪሎግራም ወርቅ ለውጭ ገበያ ቀርቦ 265.8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኝቷል። ከጌጣጌጥ ማዕድናት ደግሞ 3.215 […]
Read More
MoM