በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የከሰል ድንጋይ ፋብሪካ መሰረተ ድንጋይ ተቀመጠ

የድንጋይ ከሰልን በሀገር ውስጥ ለማምረት ላሰብነው ሀሳብ ሁለተኛውን እርምጃ ተራምደናል። በዛሬው እለትም ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ጋር በመሆን በአሶሳ ሁለተኛውን የከሰል ድንጋይ ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ አስጀምረናል ። ፋብሪካውን NOC የሚያስገነባውና በ11 ወራት የሚጠናቀቅ ይሆናል። በቀጣይ ቀናትም በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ተጨማሪ የድንጋይ ከሰል ማምረቻዎችን ግንባታ እናስጀምራለን። 
ፋብሪካዎቹ ማምረት ሲጀምሩ ሀገራዊ የማምረት አቅማችን በአመት 2.5 ሚሊዮን ቶን እሴት የተጨመረበት ( blending , washing and scrubing coal) የድንጋይ ከሰል ይሆናል።ይህ ምርት በውጪ ምንዛሪ ከውጪ የምናስገባውን የድንጋይ ከሰል በተሻለ ሁኔታ ማስቀረት የሚችል ነው።

Leave A Comment

MoM